7075 +251-11-558-8800 help@aarb.gov.et ሰኞ–ቅዳሜ | 02:30 AM – 11:30 PM
ግባ
የቢሮ ኃላፊ መልዕክት | Head's Message

መልዕክት ለግብር ከፋዮች

ወደ ዘመናዊ፣ ፍትሐዊ እና አገልጋይ ተኮር የታክስ አስተዳደር ሥርዓት

Ato Binyam Mekuru - Bureau Head
አቶ ቢንያም ምክሩ
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ
Head, Addis Ababa Revenues Bureau
የተከበራችሁ የድረ-ገጻችን ጎብኚዎች/ግብር ከፋዮቻችን

በመጀመሪያ እንኳን ወደ ድረ-ገጻችን በሰላም መጣችሁ።

ቢሯችን በታክስ ህጎች፣ አዋጆች መመሪያዎች፣ የአሰራር ማንዋሎችና መሰል መረጃዎች በቀላሉ ለእናንተ በማድረስ ስለታክስ ያላችሁ ግንዛቤ እንድታሳድጉና በተቋማችን አገልግሎትና አሰራሮች ዙሪያ ገንቢ አስተያየቶች በመስጠት ለተልዕኳችን በማሳካት የበኩላችሁን እንድትወጡ ይህንን ድረገጽ አልምተናል፡፡

አስተዳደሩ ከሚሰራቸው የከተማችን ገጽታ የሚቀይሩ ትላልቅ ፕሮጀክቶችንና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ጎን ለጎን በዝቅተኛ ገቢ የሚተዳደሩ ነዋሪዎችን ለመደገፍ በተለይም ታዳጊ ህጻናት ለማስተማርና ብሩህ ተስፋ እንዲኖራቸው ለማድረግ የምገባ፣ የዩኒፎርምና የማስተማሪያ መሳሪያዎች የማቅረብ ስራ እየሰራን እንገኛለን፡፡ እነዚህ ስራዎች የሚሰሩት ከናንተ በሚሰበሰበው ገቢ ነው፡፡ በመሆኑም የምትከፍሉት ገቢ ለሀገር እድገትና ብልጽግና ያለው ፋይዳ በመገንዘብ "ለከተማዬ እድገት የበኩሌን ልወጣ" በሚል ሀገራዊ ወይም ወገናዊ ስሜት የሚጠበቃችሁን ግብር በወቅቱ እንድትከፍሉ መልዕክቴን አስተላልፋለሁ፡፡

ለሀገር መከላከያና በተለያዩ ምክንያቶች የተነሳ ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች ለመርዳትና ለማቋቋም የሚያደረገው ድጋፍ እንደተጠበቃ፣ ግብርን በወቅቱ በመክፈል ሀገራዊ ግዴታን ለመወጣት ሌት ተቀን የሚጥሩት ታክስ ከፋዮችን እውቅና በመስጠት፣ ምርጥ ተሞክሮን በመውሰድና በማመስገን ወደ ሌሎች ማስፋት የሚገባ ሲሆን፤ በግብር መሰወር፣ ህገወጥና ያለደረሰኝ ግብይት የሚፈጽሙና ግብርን ለመክፈል ፈቃደኝነት በማጣትና በሌብነትን የተሰማሩ ጥቂት ታክስ ከፋዮች በማጋለጥና በማረም እንደሀገር ብሎም እንደ ከተማ የጀመርነው የብልጽግና ጉዞን ማሳካት ይኖርብናል፡፡

የመዋቅሩ አመራሮችና ሰራተኞችም ከታክስ ከፋዩ ህብረተሰብ የምንሰበስበው እያንዳንዱ ብር ለብልጽግና ጉዞአችን ያለው ፋይዳና ይህንን መስረቅ ደግሞ ሀገርን ማፍረስና ትውልድን መግደል መሆኑን በመገንዘብ ራሳችሁን ከህገ ወጥ ስራ በመታቀብ፣ ሌሎችን በማረምና በማጋለጥ ሀላፊነታችሁ እንድትወጡ በዚህ አጋጣሚ መልዕክቴን አስተላልፋለሁ፡፡

በመጨረሻም ይህንን ድረገጽም ሆነ ሌሎች ገጾቻችን በአግባቡ በመጠቀም የእርስ በርስ መገነባቢያ ውጤታማ የተግባቦት መንገዶች በማድረግ እንድንጠቀምባቸው አደራ እላለሁ፡፡

ፍትሃዊ የግብር አሰባሰብ ለአዲስ አበባ ብልፅግና
አቶ ቢንያም ምክሩ
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ