የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ
መሠረት እና ታሪካዊ ምዕራፎች
ዘመናዊ የግብር አስተዳደር ሥርዓት መሠረት የተጣለበት ጉዞ
የተቋሙ መሠረት እና ሕጋዊ ማዕቀፍ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ዘመናዊ የግብር አወሳሰንና አሰባሰብ ሥርዓት በመዘርጋት፣ ፍትሐዊ፣ ቀልጣፋና ጥራት ያለው አገልግሎት በመስጠት የታክስ ማጭበርበርንና ስወራን በመከላከልና በመቆጣጠር የከተማው ኢኮኖሚ የሚያመነጨውን የታክስ ገቢ በብቃትና በወቅቱ ለመሰብሰብ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስፈጻሚና ማዘጋጃ ቤት አገልግሎት አካላት እንደገና ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 64/2011 መሠረት የተቋቋመ መንግስታዊ ተቋም ነው፡፡
ተቋሙ በአዋጅ የተሰጠውን ሥልጣንና ተግባር ሲፈጽም በታክስ ህጎች ለታክስ ከፋዮች የተሠጡ መብቶችን ያከብራል፡፡ ታክስ ከፋዮችም በታክስ ህጎች መሠረት ታክስ መክፈል የዜግነት ክብር ነው በሚል መርህ ግዴታቸውን በፈቃደኝነት እንደሚወጡ ይተማመናል፡፡
ቻርተሩ በአሁን ወቅት ያለውን የተገልጋዮች ፍላጎት መሠረት በማድረግ እና የከተማ አስተዳደሩ ባደረገው የአስፈፃሚ መ/ቤቶች መዋቅራዊ ለውጥ በአዲስ መልኩ በተሰራው የመሰረታዊ የስራ ሂደት ለውጥ ጥናት /BPR/ መሰረት በተቋማችን የሚሰጡ ዋና ዋና አገልግሎቶችን በመለየት የተዘጋጀ ሲሆን ከጥር 2011 ዓ.ም ጀምሮ በሥራ ላይ ያለውን የተገልጋዮች ቻርተር አፈጻጸም ሪፖርቶች እና ተቋማዊ የተገልጋዮች እርካታ ዳሰሳ ጥናቶች የሚያሳዩትን አመላካች መረጃዎች በመጠቀምና የታዩትን ክፍተቶች በመለየት በአሁኑ ወቅት ያለውን የተገልጋዮች ፍላጎት መሠረት በማድረግ የተዘጋጀ ሲሆን ወደፊትም የሚከሰቱ መዋቅራዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ቴክኖሎጂያዊ ለውጦችን መሠረት በማድረግ የተገልጋዮችን ፍላጎት ለማሟላት በሚያስችል ሁኔታ የሚከለስና የሚሻሻል ይሆናል፡፡
ይህ የተገልጋዮች ቻርተር ከላይ በተገለጸው መሠረተ ሃሳብ ላይ በመመርኮዝ የተገልጋዮችን መብቶችና ግዴታዎች በግልጽ በማስቀመጥ ተገልጋዮች ከቢሮው የሚያገኙዋቸውን አገልግሎቶችና የአገልግሎት አሰጣጥ ስታንዳርዶችን ለማሳወቅና በዚህ መሰረት አገልግሎት ለመስጠት ያለውን ቁርጠኝነት ለመግለጽ የተዘጋጀ ሠነድ ነው፡፡
በመሆኑም የቢሮው ዓላማዎች ስልጣንና ተግባር፣ ራዕይ፣ ተልዕኮ፣ እሴቶች፣ የመ/ቤቱ ተገልጋዮች፣ የሚሰጡ የአገልግሎት ዓይነቶች፣ አገልግሎቶቹ የሚሰጡባቸውን ቦታዎችና ስታንዳርድ፣ የተገልጋዮችን መብትና ግዴታዎች፣ አስተያየት ወይም ግብዓት የሚሰጥበት ሂደት፣ የቅሬታ አቀራረብ፣ ክትትልና የግምገማ ሥርዓት፣ እንዲሁም መረጃ የሚሰጥበትን መንገዶች እና ተጠያቂነት በቻርተሩ ውስጥ የተካተቱ ዋና ዋና ጉዳዮች ናቸው፡፡
ከመሠረት ወደ ዘመናዊነት
የተገልጋዮች ቻርተር ሥራ ላይ ዋለ፣ የአገልግሎት ስታንዳርድ መሠረት ተጣለ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስፈጻሚ አካላት እንደገና ማቋቋሚያ አዋጅ - የገቢዎች ቢሮ መሠረት።
ዲጂታል የግብር ክፍያ ሥርዓት ሙከራ፣ ኢ-ቲን መድረክ መጀመር።
ዘመናዊ BPR ትግበራ፣ የአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያ።
አዲስ የታክስ አዋጅ ማሻሻያ፣ በዘመናዊነት የታከለ የደንበኞች ድጋፍ አገልግሎት መጀመር።
ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ ለአዲስ አበባ ብልፅግና